
በኤስ ኤን ቪ (SNV) ሊዌይ (LIWAY) ፕሮጀክት አዘጋጅነት፤ ለ “MSMEs የፋይናንስ በሮችን መክፈት፤በኢትዮጵያ በሴቶች÷ወጣቶችና አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ያሉ ተግዳሮቶች እና ዕድሎች” በሚል መሪ ሐሳብ፤ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ጥቃቅን አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች (MSMEs) የፋይናንስ ተደራሽነትን የሚመለከት ታላቅ ዓለም አቀፍ ሲምፖዚየም ታኅሣሥ 08/2018 ዓ.ም በሃያት ሪጄንሲ ተካሄደ፡፡
ሲምፖዚየሙም ቁልፍ የፋይናንስ ዘርፍ ባለድርሻ አካላትን ማለትም ባንኮችን÷ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትን እና ፊንቴክ ኩባንያዎችን በአንድነት በማሰባሰብ የዘርፉን ተግዳሮቶች እና ዘላቂ መፍትሔዎች ላይ ለመወያየት ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ባንካችንም በጥቃቅን÷አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ እና የገጠር ባንኪንግ መምሪያው ያሉትን አገልግሎቶች በማቅረብ እና በማስተዋወቅ ተሣተፊ ሆኗል፡፡