
አሐዱ፡ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ፤ ከሳሮ ኢትዮጵያ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ክቡሩን የሰው ሕይወት ለመታደግ በአያሌው የሚያግዘውን የደም ልገሳ መርሐ-ግብር ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም አካሒዷል፡፡
በዚህም፤ ባንኩ ካሉት ስድስት ዕሴቶች መካከል አንዱ የሆነውን የሰብአዊነት ልዩ ዕሴቱን ተግባር ላይ አውሏል፡፡ የደም ልገሳ መርሐ-ግብሩ በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት በዛሬው ዕለት ሲከናወን፤ የአሐዱ:ባንክ የሥራ አመራሮች እና ሠራተኞች ደም በመለገስ ተሣትፈውበታል፡፡