ባንካችን ብሥራተ ገብርኤል ቅርንጫፍ ተመርቆ በይፋ ሥራ ጀመረ! Dawit Addis September 16, 2025

ባንካችን ብሥራተ ገብርኤል ቅርንጫፍ ተመርቆ በይፋ ሥራ ጀመረ!

በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሕንጻ ላይ የሚገኘው 103ኛው የባንካችን ቅርንጫፍ፤ የባንካችን የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ሰብስቤ÷ ሌሎች የቦርድ አባላት÷የባንካችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉጌታ በዛ÷የባንካችን ከፍተኛ የሥራ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በታደሙበት፤ በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አባቶች ጸሎት እና ቡራኬ ተመርቆ መስከረም 03/2018 ዓ.ም በይፋ ሥራ ጀመረ::

በዕለቱም የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ሰብስቤ፤ ቅርንጫፎችን እንዲህ የምንከፍተው ኢትዮጵያውያንን/ትን በክብር ለማገልገልና ነውና ሁላችንም ሒሳብ በመክፈት እና አክሲዮን በመግዛት እንገልገልበት ብለዋል::

የባንካችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉጌታ በዛ በበኩላቸው፤ ከብዙዎች ለብዙዎች በሚል መርሕ ተግባሩን እየከወነ የሚገኘው ባንካችን ለብዙዎች ለመድረስ እየተጋ በመሆኑ፤ በትብብር በመሥራት ባንካችንን ወደ ሚፈለገው ውጤት ማድረስ ይጠበቅብናል በማለት ተናግረዋል::