የአሐዱ፡ባንክ የ2017 ዓ/ም ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ጉባዔ የታለመለትን ግብ በማሳካት ተጠናቀቀ! Dawit Addis September 5, 2025

የአሐዱ፡ባንክ የ2017 ዓ/ም ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ጉባዔ የታለመለትን ግብ በማሳካት ተጠናቀቀ!

ጉባኤው ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እንደ መሆኑ መጠን፤ ለውይይት የያዛቸው አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ጉባዔውን አጠናቋል፡፡
ይኽ በእንዲህ እንዳለ፤ ባንኩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት (እ.ኤ.አ. 2024/25) አመርቂ አፈጻጸም አሳይቷል፡፡ በዚህም መሠረት፡-

  • ከብር 2.1 ቢሊዮን በላይ ገቢ በመሰብሰብ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት የብር 1 ቢሊዮን ጭማሪ ወይንም 90.9 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል፡፡
  • የእርጅና ተቀናሽን ጨምሮ ከተያያዥ ወጪዎች በኋላ እንዲሁም ከመጠባበቂያና ግብር በፊት ብር 569 ሚሊዮን ያተረፈ ሲሆን፤ ይኽም ከአምና ተመሳሳይ ወቅት የብር 450 ሚሊዮን ብልጫ ወይም 278.1 በመቶ እድገት አስመዝግቧል፡፡
  • የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ ብር 7.8 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን፤ ይኽም ከባለፈው በጀት ዓመት አንጻር የ68 በመቶ እድገት አስመዝግቧል፡፡
  • በውጭ ምንዛሬ ገቢ ረገድ ከUSD 88 ሚሊዮን በላይ መሰብሰብ ተችሏል፡፡
  • አጠቃላይ ሀብቱም የ57 በመቶ እድገት በማስመዝገብ ከብር 10 ቢሊዮን በላይ በማድረስ ከፍተኛ ዕመርታን አሳይቷል፡፡
  • የደንበኞቹን ቁጥር ከ1 ሚሊዮን በላይ አድርሷል፡፡
    በአጠቃላይ፤ አሐዱ፡ባንክ እ.ኤ.አ. ሰኔ 30 የተጠናቀቀውን የ2024/25 የበጀት ዓመት በአንፀባራቂ ስኬቶች ታጅቦ ማጠናቀቁን ስናበሥር ታላቅ ደስታ ይሰማናል፡፡
    ለዚህ ስኬት የጎላ አስተዋፅኦ ላደረጋችሁልን ክቡራን/ት ደንበኞቻችን፣ ባለአክሲዮኖቻችን፣ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድና የሥራ አመራር አባላት፣ ሠራተኞቻችን እንዲሁም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት እያመሰገንን፤ በአዲሱ በጀት ዓመት ጠንክረን በመሥራት ከዚህ የላቀ ስኬት የምናስመዘግብበት እንደሚሆን ሙሉ እምነት አለን፡፡

Write a comment
Your email address will not be published. Required fields are marked *